
ምርጫ 97፡ ከ20 ዓመታት በኋላ ሲታወስ
በኢትዮጵያ የምርጫ ታሪክ በብዙ መልኩ የተለየ የነበረው ምርጫ 97 ከተካሄደ እነሆ ዛሬ 20 ዓመቱን ደፈነ። ገዢው ኢህአዴግ 'እንከን የለሽ' ዴሞክራሲያዊ ምርጫ ለማካሄድ ቃል መግባቱን ተከትሎ ተቃዋሚዎች ጥምረት ፈጥረው የተካሄደው ምርጫ ቃል እንደተገባለት ሳይሆን ቀውስን አስከትሎ ነበር የተጠናቀቀው። ኢትዮጵያም ወደ ዴሞክራሲ ልታመራ የምትችልበት ዕድል ጨንግፎ ኢህአዴግ ሁሉን ተቆጣጥሮ ወደ በለጠ ፈላጭ ቆራጭነት አመራ። ከዚያም በኋላ ሕዝቡ ነጻ እና ዴሞክራሲያዊ ምርጫ እንደናፈቀ ሁለት አስርት ዓመታት ተቆጠሩ።
Read the full story