
በምርጫ ለመሳተፍ በቅድመ ሁኔታ እና ሕጋዊነትን በማጣት መካከል የተወጠሩት የፖለቲካ ፓርቲዎች
አስር ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ በዚህ ዓመት የሚካሄደው ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ እንዲሆን እና "ከአጃቢነት ያለፈ ተሳትፎ" እንዲኖራቸው የሚጠይቅ ቅድመ ሁኔታዎችን አቀረቡ። ራሳቸውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች አንድነት መድረክ (መድረክ) ሲሉ የሚጠሩት 10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ ኅዳር 3/2018 ዓ.ም. በጋራ ባወጡት መግለጫ ላይ "ሕጋዊነትን ለመላበስ የሚደረጉ የፖለቲካ ትወናዎች" ሲሉ ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎችን በመኮነን፤ ምርጫዎቹ "ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አሳታፊ፤ በውጤታቸውም ተዓማኒ እና በሕዝብ ተቀባይነት አላገኙም" ሲሉ ተችተዋል።
Read the full story