
'ቤተሰቦቼ ከሞትኩ በኋላ መርዶ ቢነገራቸው ይሻላል' - በሳዑዲ እስር ቤቶች የሞት ቅጣት የሚጠባበቁት ኢትዮጵያውያን
በሳዑዲ አረቢያ ሦስት ኢትዮጵያውያን ከአደንዛዥ ዕጽ ጋር በተያያዘ ክስ የሞት ፍርድ ሲፈጸምባቸው ቢያንስ 65 የሚሆኑት ደግሞ ፍርዳቸው ተፈጻሚ የሚሆንበትን ጊዜ እየተጠባበቁ መሆኑን ሂውማን ራይትስ ዎች አስታውቋል። የሳዑዲ መገናኛ ብዙኃን በካሃሚስ ሙሻይት ማረሚያ ቤት የሚገኙ ከ200 በላይ ኢትዮጵያውያን የሞት ፍርድ እየጠበቁ መሆኑን ዘግበዋል። ቢቢሲ ያነጋገራቸው የሞት ፍርድ የተፈረደባቸው እነዚህ ወጣቶች ከመርፈዱ በፊት የኢትዮጵያ መንግሥት ይድረስልን ሲሉ ይማጸናሉ።
Read the full story