
የኤርትራ መንግሥት ዜጎች በእጃቸው ያለ ገንዘብን በአንድ ወር ወደ ባንክ እንዲያስገቡ አዘዘ
የኤርትራ መንግሥት ዜጎቹ በእጃቸው ላይ ያለ ገንዘብን በሙሉ እስከ ሐምሌ መጨረሻ ድረስ ወደ ባንክ እንዲያስገቡ ጥብቅ ማሳሰቢያ አወጣ። የኤርትራ ማዕከላዊ ባንክ ማክሰኞ ዕለት ባወጣው ጥብቅ ማሳሰቢያ፤ በአገሪቱ ውስጥ በግለሰቦች እና በተቋማት እጅ የሚገኝ የአገሪቱ መገበያያ ገንዘብ (ናቅፋ) በሙሉ ዛሬ የጀመረው የአውሮፓውያን ሐምሌ ወር መጠናቀቂያ ድረስ ወደ ባንክ እንዲገባ አዝዟል።
Read the full story