
የተከፋፈሉት የህወሓት አመራሮች ለፖለቲካ ግቦቻቸው "ኃይል ላለመጠቀም" መፈራረማቸው ተገለጸ
ክፍፍል እና እሰጣገባ ውስጥ ያሉት ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) አመራሮች የፖለቲካ ግቦቻቸውን ለማሳካት "ኃይልን ላለመጠቀም" መፈራረማቸውን የትግራይ የሃይማኖት አባቶች ይፋ አደረጉ። ለሁለት የተከፈለው ህወሓት አመራሮች የሆኑት የአቶ ጌታቸው ረዳ እና የዶ/ር ደብረፅዮን ገብረሚካኤል ፊርማ ያረፈበት ይህ ሰነድ፣ አንዳቸው በሌላኛቸው ላይ "የበላይነት ለማረጋገጥ ወደ ማንኛውም ዓይነት የአመጽ ተግባር" እንደማይገቡ የሚገልጽ ነው።
Read the full story