
በትግራይ በተካሄዱ ሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ክስ የቀረበባቸው ኮሎኔል ተወልደ ምን ይላሉ?
የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር የቀድሞ ፕሬዚዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ በቅርቡ ከፋና ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር እና የወርቅ ማዕድን ማውጣት ላይ ተሰማርተዋል ሲሉ ከከሰሷቸው የቀድሞ የስራ ባልደረቦቻቸው መካከል የትግራይ ኃይሎች የመረጃ መምሪያ ኃላፊ የነበሩት ኮሎኔል ተወልደ ገብረትንሳዔ አንዱ ናቸው። ቢቢሲ ትግርኛ በሕገወጥ የሰዎች ዝውውር ስማቸው የተጠቀሰውን ኮሎኔል ተወልደን ያናገረ ሲሆን፤ እሳቸውም "ስሜ ጠልሽቷል" ሲሉ የቀረበባቸውን ውንጀላ አስተባብለዋል።
Read the full story