በትግራይ ክልል የተረቀቀው እና ስጋት የፈጠሩት በሞት የሚያስቀጡት አንቀጾች
በቅርቡ በማኅበራዊ ሚዲያ እየተሠራጨ ያለው እና ከስድስት ዓመት በፊት በተደረገው እና ለጦርነቱ እንደ አንድ ምክንያት በሚጠቀሰው ምርጫ የተቋቋመው የትግራይ ክልል አስተዳደር እንዳረቀቀው የሚነገርለት አዲሱ ረቂቅ አዋጅ አወዛጋቢ ሆኗል። "የትግራይ ሕዝብ ኅልውና እና ደኅንነትን ለማረጋገጥ የትግራይ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት ያወጣው አዋጅ" በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ይህ ረቂቅ ሰነድ በክልሉ ምክር ቤት እንደሚጸድቅ ቢቢሲ ትግርኛ ከምንጮቹ ያገኘው መረጃ ያሳያል።









