"ሙስሊም ነኝ፤ እንዳትተኩሱብኝ": ከሆርሙዝ መዘጋት ቀጥሎ በሶማሊያ ያገረሸው የባሕር ላይ ውንብድና
በባሕረ ሰላጤው በኢራን ላይ ጦርነት ከተከፈተ በኋላ ዋነኛው የነዳጅ መተለላፊያ የሆርሙዝ ወሽመጥ በመዘጋሩ በኃይል አቅርቦት ላይ ቀውስ ተፈጥሯል። ይህንን ተከትሎ ደግሞ ጋብ ብሎ የነበረው የሶማሊያ የባሕር ላይ ወንበዴዎች በመርከቦች ላይ የሚፈጽሙት ዕገታ አገርሽቷል። ይህም በሌላኛው የባሕር መተላለፊያ ቀይ ባሕር መግቢያ ላይ እየተከሰተ ያለው የባሕር ላይ ውንብድና ከፍተኛ ስጋትን ፈጥሯል።








