አራት ሺህዎቹ የሀገራዊ ምክክር ተሳታፊዎች በአጀንዳዎች ላይ የሚወያዩት እንዴት ነው?
የሀገራዊ ምክክር ኮሚሽን ከአራት ዓመት በላይ ከወሰደ የተወካዮች መረጣ፣ አጀንዳ ማሰባሰብ እና ሌሎች ተግባራት በኋላ ዛሬ ረቡዕ ሐምሌ 8/2018 ዓ.ም. የመጨረሻውን የሀገራዊ ምክክር ጉባኤ ያስጀምራል። በአዲስ አበባ ከተማ 'አዲስ ኮንቬንሽን ሴንተር' በሚካሄደው በዚህ ጉባኤ ላይ ከተለያዩ ክልሎች፣ ወረዳዎች፣ ከፌደራል እንዲሁም በውጭ አገራት ከሚኖሩ ኢትዮጵያውያን የተወጣጡ ከአራት ሺህ ሰዎች ይሳተፋሉ።









