በኢትዮጵያ በአደጋ ሙሉ በሙሉ የተቆረጠ ክንድ እንዴት በተሳካ ሁኔታ ተመልሶ ሊገጠም ቻለ?

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day






የገንዘብ ሚኒስቴር የንብረት ታክስ የሚጣልበትን እና የሚሰበሰብበትን መንገድ በተመለከተ ዝርዝር መረጃዎችን የያዘ "ሞዴል" ረቂቅ ሕግ በታኅሣሥ 2018 ዓ.ም. መጀመሪያ ወደ ክልል እና ከተማ አስተዳደሮች ልኳል። የንብረት ታክስን የመጣል እና የመሰብሰብ መብት የክልሎች ቢሆንም ከግብሩ ጋር ለሚያወጡት ሕግ "መነሻ የሚሆን ሞዴል" ረቂቅ ሕግ የሚዘጋጀው በፌደራል መንግሥት እንደሆነ የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ደብዳቤ ያስረዳል።


በትግራይ ክልል በሰሜናዊ ምዕራብ አካባቢ ካሉት የተፈናቃይ ካምፖች መካከል አንዱ በሆነው ሕጻጽ በርካቶች በረሃብ ውስጥ መሆናቸውን ተናገሩ። ተፈናቃዮቹ በእርዳታ የሚደርሳቸው ምግብ ድጋፍ በቂ ካለመሆኑም በላይ ከፍተኛ የጥራት ችግር እንዳለበት ገልጸዋል። በምዕራብ ትግራይ በመቶዎች የሚቆጠሩ ተፈናቃዮች በሰብዓዊ እርዳታ አቅርቦት እጥረት ምክንያት "በረሃብ እና በበሽታ" የመጠቃት አደጋ እንደተጋረጠባቸው ተናግረዋል።

