አሜሪካ፤ በብሔራዊ ዘብ አባላት ላይ በደረሰው ጥቃት ምክንያት የአፍጋኒስታናውያንን የስደተኝነት ጥያቄ አገደች

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day

REACT 2.0 opens applications for Ethiopian firms working on PUE tech like irrigation, cooling, solar energy, and milling. Up to $400k grants available via milestone-based funding. By Etenat AwolEthiopia’s central bank to inject $520M into FX market through Dec–Mar auctions as birr shows measured depreciation By Team Shega

ሃይሊ ጉቢ እሳተ ገሞራ የፈነዳው ከ12ሺህ ዓመታት በኋላ ነው። እስከባለፈው እሑድ ድረስ አንዳችም እንቅስቃሴ ሳያሳይ ቆይቷል። የእሳተ ገሞራው አመድ በነፋስ አማካይነት አንድ ሺህ ጫማ ተጉዞ ጥቃቅን ቅንጣቶች ሰማይ ላይ ታይተዋል። ለመሆኑ ንቁ እሳተ ገሞራ እና ለዘብተኛ እሳተ ገሞራን ምን ይለያቸዋል? እሳተ ገሞራ ሊፈነዳ ሲል የሚያሳያቸው ምልክቶችስ የትኞቹ ናቸው?


ምሥራቅ አፍሪካዊቷ አገር ኡጋንዳ የአፍሪካ ቀንድ አገራት ከሆኑት ከኢትዮጵያ፣ ከኤርትራ እና ከሶማሊያ ለሚመጡ ሰዎች የስደተኝነት ምዝገባ ማቆሟን አስታወቀች። ይህ ውሳኔ የተሰማው ወደ ኡጋንዳ የሚገቡ ስደተኞች ቁጥር በከፍተኛ ሁኔታ በጨመረበት እና ከለጋሾች ለስደተኞች ተብሎ የሚመጣው ድጋፍ በመቀነሱ እንደሆነ ተዘግቧል።

የጊኒ ቢሳዎ ወታደሮች በአገሪቱ የፕሬዝዳንት ምርጫ ከተካሄደ ከሦስት ቀናት በኋላ ፕሬዝዳንቱን በቁጥጥር ስር አውለው መላዋ አገሪቱን መቆጣጠራቸውን አስታወቁ። የጦር መኮንኖቹ ፕሬዝዳንት ኦማሮ ሲሶኮ ኤምባሎን መያዛቸወን ያስታወቁት ረቡዕ ከሰዓት በኋላ በዋና ከተማዋ ቢሳዎ በፕሬዝዳንታዊው ቤተ መንግሥት ውስጥ ከባድ ተኩስ ከተሰማ በኋላ ነው።




