ደቡብ አፍሪካ ፍልስጤማውያንን የጫነ አውሮፕላን ስለመጣበት "ምሥጢራዊ" መንገድ ምርመራ እንደምታካሂድ አስታወቀች

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day






ኡጋንዳን አራት አስርት ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ የመሩት ፕሬዝዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ አገራቸውን ወደ ሕንድ ውቅያኖስ የሚያደርስ የባሕር በር እና የባሕር ኃይል እንዲኖራቸው እንደሚፈልጉ በይፋ ተናግረዋል። ይህ የፕሬዝዳንቱ ፍላጎት ደግሞ ያነጣጠረው በጎረቤት ኬንያ ላይ መሆኑ በኬንያውያን ዘንድ መነጋገሪያ ሆኗል። ሙሴቬኒ አገራቸው የባሕር መተላለፊያ ካላገኘች በአካባቢው ወደፊት ለሚከሰት ጦርነት ምክንያት ሊሆን እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።


ኤርትራ በኢትዮጵያ "ሉዐላዊነት እና የግዛት አንድነት" ላይ የምትፈጽማቸው "ጥሰቶችን" በተመለከተ የፌደራል መንግሥት የያዘው እርምጃ ከመውሰድ "የመታቀብ" አካሄድ "ሁሌም የሚቀጥል እና ገደብ የለሽ ተደርጎ መወሰድ እንደሌለበት" የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዶ/ር ጌዲዮን ጢሞቲዎስ ተናገሩ። ዶ/ር ጌዲዮን፤ ኢትዮጵያ "ከኤርትራ መገንጠል በፊት እና በኋላ" በአሰብ ወደብ ላይ "ባፈሰሰችው ከፍተኛ ሀብት ምክንያት"፤ አሰብ በፌደራል መንግሥት "በዋነኛነት ቅድሚያ የሚሰጠው" ጉዳይ እንደሆነ መግለጻቸውም ተዘግቧል።

