ታግቶ የተወሰደው የመተማ ሆስፒታል ሐኪም የተጠየቀው ገንዘብ ቢከፈልለትም ተገድሎ ተገኘ

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day

አስር ተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ በዚህ ዓመት የሚካሄደው ምርጫ ነፃ፣ ፍትሃዊና ተዓማኒ እንዲሆን እና "ከአጃቢነት ያለፈ ተሳትፎ" እንዲኖራቸው የሚጠይቅ ቅድመ ሁኔታዎችን አቀረቡ። ራሳቸውን የኢትዮጵያ ፖለቲካ ፓርቲዎች አንድነት መድረክ (መድረክ) ሲሉ የሚጠሩት 10 የተቃዋሚ ፓርቲዎች ስብስብ ኅዳር 3/2018 ዓ.ም. በጋራ ባወጡት መግለጫ ላይ "ሕጋዊነትን ለመላበስ የሚደረጉ የፖለቲካ ትወናዎች" ሲሉ ከዚህ ቀደም የተደረጉ ምርጫዎችን በመኮነን፤ ምርጫዎቹ "ነፃ፣ ፍትሃዊ እና አሳታፊ፤ በውጤታቸውም ተዓማኒ እና በሕዝብ ተቀባይነት አላገኙም" ሲሉ ተችተዋል።

በሕገ ወጥ የውጭ ምንዛሪ አሻጥሮችን ሲፈጽሙ ነበር የተባሉ በርካታ ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ሥር መዋላቸውን እና ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው የባንክ አካውንቶች መታገዳቸውን የመንግሥት የፀጥታ እና ደኅንነት አካላት አስታወቁ። የብሔራዊ መረጃ እና ደኅንነት አገልግሎት፣ የፋይናንስ ደኅንነት አገልግሎት፣ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ እና የክልል የፀጥታ ተቋማት በወሰዱት እርምጃ በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር ላይ ተሳትፈዋል ተብለው የተጠረጠሩ ግለሰቦች እና አካወንቶች ናቸው ለእስር እና ለዕግድ የበቁት።





የቢቢሲ ዋና ዳይሬክተር ቲም ዴቪ እና የዜና ዋና ኃላፊዋ ዴብራ ተርነስ በአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዙሪያ ከተሰራ ዘጋቢ ፊልም ጋር በተያያዘ ኃላፊነታቸውን ለቀቁ። ሁለቱ ኃላፊዎች የፕሬዚዳንቱን ንግግር በመቆራረጥ ተመልካቾችን አሳስተዋል የሚል ትችት ከቀረበባቸው በኋላ ከኃላፊነት መልቀቃቸውን ገልፀዋል። ሾልኮ የወጣ ነው የተባለው እና ቴሌግራፍ ያወጣው ጽሑፍ የፕሬዚዳንት ትራምፕ ሁለት ንግግሮች ተቆርጠው የተቀጠሉ ሲሆን፣ በዚህ ንግግርም ትራምፕ የካፒቶል ሂልን አመፅ እንደደገፉ አድርጎ ማሳየቱን ጠቁሟል።


