ፈረንሳይ ውስጥ በሁለት ሳምንት ልዩነት ሌላ ግዙፍ ዝርፊያ ተፈጸመ

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day




ሰሞኑን አረቄ ብሔራዊ አጀንዳ ሆና የማኅበራዊ ሚዲያ አናት ላይ ወጥታ ነበር። ጠጅ ቢሆን አናት ላይ አይወጣም፤ ወደ ጉልበት ነው የሚወርደው። ጠጅ ለመጨረሻ ጊዜ ጉዳይ ሆኖ የሥነ መንግሥቱ አናት ላይ ወጥቶ፣ 'ብሔራዊ አጀንዳ' የነበረው በዐፄ ዮሐንስ 4ኛ ዘመን ነው። ድሮ ጠጅ በብርሌ ይቀርብ ነበር። ከዚያ በብርሌ ይጠጣ ጀመር። ጠጅ ግን እንደ አረቄ ማንም ‘ተራ ዜጋ’ ብድግ አድርጎ አያንደቀድቀውም።ብርሌ ውስጥ የመደብ ታሪክ አለ። የዘመን ታሪክ አለ። የጭሰኛና የመሳፍንት ታሪክ አለ። ያልተሳከረ።




ፕሬዝዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ ከኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በካይሮ ባደረጉት ውይይት ግብፅ የኤርትራን ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት በፅኑ እንደምትደግፍ ተናገሩ። ለአምስት ቀን የሥራ ጉብኝት ሐሙስ ጥቅምት 20 2018 ዓ.ም. ካይሮ የደረሱት የኤርትራው ፕሬዝዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ከግብጹ አቻቸው ጋር በተለያዩ ጉዳዮች መወያየታቸው ተገልጿል። የፕሬዝዳንት ኢሳያስ ጉዞ የመጣው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት የቀይ ባሕር ለኢትዮጵያ "ሕጋዊ፣ ታሪካዊ፣ መልክዓ ምድራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳይ ነው" በማለት ከተናገሩ በኋላ ነው።

