ይዞታውን እያሰፋ ያለው አልሻባብ ለሶማሊያ መንግሥት ኅልውና ያሰጋል?
ባለፉት ዓመታት እየተዳከመ ከዋና ዋና ከተሞች ውጪ በመሆን ላይ የነበረው እና ከአል-ቃኢዳ ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚነገርለት ታጣቂው የሶማሊያ ቡድን አልሻባብ እያንሰራራ ነው። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ኅብረት ኃይሎች ድጋፍ ከዓመታት በፊት ከቡድኑ ነጻ የሆኑ አካባቢዎችን ከመንግሥት ኃይሎች ነጥቆ በመቆጣጠር ላይ ነው። የሶማሊያ መንግሥት ፖለቲካዊ አለመረጋጋት አልሻባብን እንዲጠናከር እያደረገው መሆኑን ተንታኞች ይናገራሉ።

