የእስራኤል ፕሬዝዳንት እንዲሆን ተጠይቆ የነበረው ታዋቂው የፊዚክስ ሊቅ አልበርት አንስታይን

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day
የኢትዮጵያ መንግሥት ተጨማሪ እሴት ታክስን (ቫት) ወደ 17.5 በመቶ እንዲያሳድግ ቀረበለትን ምክረ ሀሳብ ተግባራዊ እንደማያደርግ ጠቆመ። መንግሥት በዚህ ዓመት አዋጁን ሲያሻሽል የተጨማሪ እሴት ታክስ ምጣኔ 15 በመቶ ሆኖ እንዲቀጥል" መወሰኑን የገንዘብ ሚኒስቴር ገልጿል። የፌደራል መንግሥት ይህንን ውሳኔ ያስተላለፈው ቫትን አሁን ካለበት "15 በመቶ ከፍ እንዲል ማድረግ ጫና" ሊፈጥር እንደሚችል የቀረበለትን ምክረ ሀሳብ በመቀበል መሆኑን ገልጿል።

በደቡብ ትግራይ በራያ አዘቦ ወረዳ መኾኒ ከተማ በክልሉ ፀጥታ ኃይሎች እና ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን ቢቢሲ ትግርኛ ከነዋሪዎች፣ ከቤተሰቦች እና ከሕክምና ባለሙያዎች ሰምቷል። ጥቃቱ የተፈጸመው በትግራይ "አርሚ 43" ዕዝ አባላት እና ኮር ሁለት ታጣቂዎች መካከል በተፈጠረ ግጭት መሆኑን የዓይን እማኞች ይናገራሉ።




ለረዥም ጊዜ በተለያዩ መድረኮች አብሮት የሠራው ፀሐፌ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፣ ደበበን ሲያስታውሰው "የኪነጥበብ ሕይወታችን ለውጭው ዓለም ካስተዋወቁልን የጥበብ ሰዎች መካከል አንዱ" ይለዋል። በምርጫ 97 ዋነኛ የፖለቲካ ተፎካካሪ የነበረው ቅንጅት ለአንድነት ለዲሞክራሲ ፓርቲ ውስጥ አባል የነበረችው እና አብራው የተለያዩ የፖለቲካ ሥራዎችን የሠራችው ብርቱካን ሚደቅሳ ደግሞ "ፖለቲካን ከተለመደው መልኩ በተለየ መንገድ መሥራት የቻለ" ስትል ያላትን አክብሮት ትገልጻለች።



ባለፉት ዓመታት እየተዳከመ ከዋና ዋና ከተሞች ውጪ በመሆን ላይ የነበረው እና ከአል-ቃኢዳ ጋር ግንኙነት እንዳለው የሚነገርለት ታጣቂው የሶማሊያ ቡድን አልሻባብ እያንሰራራ ነው። በአሁኑ ወቅት በአፍሪካ ኅብረት ኃይሎች ድጋፍ ከዓመታት በፊት ከቡድኑ ነጻ የሆኑ አካባቢዎችን ከመንግሥት ኃይሎች ነጥቆ በመቆጣጠር ላይ ነው። የሶማሊያ መንግሥት ፖለቲካዊ አለመረጋጋት አልሻባብን እንዲጠናከር እያደረገው መሆኑን ተንታኞች ይናገራሉ።
