አሜሪካ በትግራይ የሰላም ሂደትን "የሚያደናቅፉ አካላትን" አሳሰበች
በትግራይ የሰላም ሂደትን "እያደናቀፉ ያሉ አካላት" ለውይይት ጥረቶች ትብብር እንዲያደርጉ በአዲስ አበባ የአሜሪካ ኤምባሲ ማሳሰቢያ ሰጠ። በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ፣ የፖለቲካ እና የሲቪል ማኅበረሰብ መሪዎች በፖለቲካ ውይይት ውስጥ መሳተፍ እና የፕሪቶሪያውን ግጭትን በዘላቂነት የማቆም ስምምነት ሙሉ በሙሉ መተግበር እንዳለባቸው አሳስቧል።









