የቀድሞው የኤፍቢአይ ዳይሬክተር ምክር ቤት በመዋሸት ለቀረበባቸው ክስ ጥፋተኛ አይደለሁም አሉ

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day




ከትግራይ ክልል ተወክለው የፕሪቶሪያ ስምምነት ተፈራራሚ ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት አቶ አሰፋ አብርሃ በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ውጊያ ሊነሳ የሚችልበት ዕድል "ያለ አይመስለኝም" ብለዋል። አቶ አሰፋ ከቢቢሲ ትግርኛ ጋር በትግራይ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ባደረጉት ቃለ ምልልስ ኢትዮጵያ እና ኤርትራ ወደ ጦርነት ሊገቡ አይችሉም ያሉበትን ምክንያት ሲያስረዱ ሁለቱ መሪዎች ሳዑዲ አረቢያ፣ የተባበሩት አረብ ኤምሬትስ እንዲሁም "ዓለም በሙሉ ባለበት የፈረሙት ስምምነት አላቸው" በማለት አብራርተዋል።


የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የኤርትራ መንግሥት እና ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) በጋራ በመሆን "ጽምዶ" በሚል ጥምረት ኢትዮጵያ ላይ "ጦርነት ለመክፈት" እየሰሩ መሆናቸውን ገለፀ። ሚኒስቴሩ ለተባበሩት መንግሥታት በፃፈው ደብዳቤ ሁለቱ አካላት በቅርቡ የፋኖ ታጣቂዎች በሰሜን ወሎ ዞን የምትገኘውን ወልዲያን ከተማ ለመቆጣጣር ባደረጉት ሙከራ ውስጥ ተሳትፈዋል ሲል ወንጅሏቸዋል።

