በኩባ "ለማኝ የለም" ያሉት ሚኒስትር በበረታባቸው ጫና ከስልጣን ለቀቁ
በኩባ "ለማኝ የለም" ብለው የተናገሩት የአገሪቱ የሰራተኛ ሚኒስትርታ ኢሌና ፌይቶ ካብሬራ በደረሰባቸው ጫና ምክንያት ከስልጣን ለመልቀቅ መገደዳቸው ተገለጸ።

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day
በኩባ "ለማኝ የለም" ብለው የተናገሩት የአገሪቱ የሰራተኛ ሚኒስትርታ ኢሌና ፌይቶ ካብሬራ በደረሰባቸው ጫና ምክንያት ከስልጣን ለመልቀቅ መገደዳቸው ተገለጸ።


በአማራ ክልል ማዕከላዊ ጎንደር ዞን ታጣቂዎች በፈጸሙት ጥቃት ዘጠኝ ሰዎች መገደላቸውን እና ሕጻናትን ጨምሮ ስድስት ሰዎች መታገታቸውን የሟች ቤተሰቦች፣ ነዋሪዎች እና የአካባቢው ባለሥልጣን ገለጹ። ነዋሪዎች እና የአካባቢው ባለስልጣን፤ የቅማንት ማኅበረሰብ መኖሪያ በሆነው ጎዶ ሞላሊት ቀበሌ ለተፈጸመው ጥቃት "የፋኖ" ታጣቂዎችን ተጠያቂ አድርገዋል።


የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢትዮጵያ ታላቁ የሕዳሴ ግድብ ላይ በሰጡት አስተያየት "ፍትሃዊ ስምምነት" እንዲደረስ ጥሪ አቅርበዋል ሲሉ የግብፁ ፕሬዚዳንት አብደል ፋታህ አል ሲሲ አወደሱ። ትራምፕ ሰኞ፣ ሐምሌ 7/2017 ዓ.ም. አሜሪካ የ[ሕዳሴ] ግድብን አገራቸው "በገንዘብ ደግፋለች" እንዲሁም ግድቡ "ወደ ናይል የሚሄደውን ውሃ የሚዘጋ" ነው የሚሉ አወዛጋቢ ንግግር ዋሺንግተን ውስጥ ማድረጋቸው ይታወሳል።




እስራኤል ለሁለት ቀናት የዘለቀውን አስከፊ የሃይማኖት ግጭት ተከትሎ የድሩዝ ህዝቦች በብዛት ወደሚኖሩባት ከተማ እየገቡ የነበሩ የሶሪያ መንግስት ወታደሮች ላይ በሱዌይዳ ዙሪያ የቦምብ ድብደባ መፈጸሟን ተናገረች።

