ትራምፕ ከኔቶ ዋና ፀሐፊ ጋር ስለ ግብፅ እና [ሕዳሴ] ግድብ ምን አሉ?
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ በዩክሬን ግጭት ላይ በ50 ቀናት ስምምነት ላይ ካልደረሰች ማዕቀብ እንደሚጣልባት ባስፈራሩበት ንግግራቸው፤ የ[ሕዳሴ] ግድብን አገራቸው "በገንዘብ ደግፋለች" እንዲሁም ግድቡ "ወደ ናይል የሚሄደውን ውሃ የሚዘጋ" ሲሉ አወዛጋቢ ንግግሮችን አድርገዋል።

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day
የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ሩሲያ በዩክሬን ግጭት ላይ በ50 ቀናት ስምምነት ላይ ካልደረሰች ማዕቀብ እንደሚጣልባት ባስፈራሩበት ንግግራቸው፤ የ[ሕዳሴ] ግድብን አገራቸው "በገንዘብ ደግፋለች" እንዲሁም ግድቡ "ወደ ናይል የሚሄደውን ውሃ የሚዘጋ" ሲሉ አወዛጋቢ ንግግሮችን አድርገዋል።

በኦሮሚያ እና በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች በደረሰ ጥቃት እና ይህንን ተከትሎ በተፈጸመ የአጸፋ ጥቃት ቢያንስ 24 ሰዎች መገደላቸውን የሟች ቤተሰቦች እና ነዋሪዎች ለቢቢሲ ተናገሩ። ነዋሪዎች፤ በኦሮሚያ ክልል ለተፈጸመው ጥቃት "ፋኖ" ሲሉ የጠሯቸውን ታጣቂዎች ተጠያቂ ያደረጉ ሲሆን፣ የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ነዋሪዎች ደግሞ ሌላኛው ጥቃት የተፈጸመው "በኦሮሚያ ክልል ፀጥታ ኃይሎች" እንደሆነ ተናግረዋል።

ከአራት ዓመታት በፊት በትግራይ ጦርነት ወቅት በክልሉ የሰብዓዊ ተልእኮ ላይ የነበሩ ድንበር የለሽ የሀኪሞች ቡድን (ኤምኤስኤፍ) ሶስት ሰራተኞች "ሆን ተብሎ እና በግልጽ ተለይተው" በኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት "ያነጣጠረ ግድያ" እንደተፈጸመባቸው ድርጅቱ አስታወቀ።

በዩናይትድ ኪንግደም ሁለት ጥንዶች ልጃቸውን ከመንግሥት ማደጎ ለማስመለጥ ሲሞክሩ በመሞቷ በከባድ የቸልተኝነት ግድያ ወንጀል ጥፋተኛ ተባሉ።

የታዋቂው አሜሪካዊት ሙዚቀኛ ቢዮንሴ ያልተለቀቁ ዘፈኖችን ጨምሮ ላፕቶፕ እና ሌሎች በርካታ ዕቃዎች በአትላንታ ከመኪና ውስጥ መሰረቃቸው ተገለጸ።

የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አገራቸው በኔቶ የሰሜን አትላንቲክ የጦር ቃል-ኪዳን ድርጅት) አጋርነት በኩል ለዩክሬን "ዘመናዊ የጦር መሣሪያዎችን" እንደምትልክ ሲያሳውቁ፤ ሩሲያ ጦርነቱን በ50 ቀናት ለመቋጨት ስምምነት ላይ ካልደረሰች ታሪፍ እጥላለሁ ሲሉ ዛቱ።

በህንድ ለ260 ሰዎች ህይወት መቀጠፍ መንስዔ የቦይንግ አውሮፕላን ከተነሳ ከሰኮንዶች በኋላ የነዳጅ መቆጣጠሪያዎች ጠፍተው ወደ ሞተሩ የሚደርሰው ነዳጅ መቋረጡ መሆኑን ሪፖርት መውጣት ተከትሎ፤ህንድ አየር መንገዶች የአውሮፕላኑ ነዳጅ መቆጣጠሪያዎችን በጥብቅ እንዲፈትሹ መመሪያ አወጣች ።


ዩናይትድ ስቴትስ የመጀመሪያውን የኒውክሌር ቦምብ ካፈነዳች ከሰማንያ ዓመታት በኋላ የኢራን የኒውክሌር መርሃ ግብር የመካከለኛው ምሥራቅን ወደ ግጭት ቀጣና እየቀየረው ነው።በአሁኑ ጊዜ በዓለም ላይ ዘጠኝ አገራት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ እንዳላቸው ይታወቃል። እንዴት የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ሊታጠቁ ቻሉ? ሌሎች አገራትስ መሣሪያውን ማግኘት ከፈለጉ ይህንን ማሳካት ይችላሉ?
