የሱዳን ጦር ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ቤተ መንግሥቱን መልሶ ተቆጣጠረ
የሱዳን ጦር ተፋላሚውን የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በማሸነፍ ከሁለት ዓመት ጦርነት በኋላ ካርቱም የሚገኘውን ፕሬዚዳንታዊ ቤተ መንግሥት መልሶ መቆጣጠሩን ወታደራዊ መሪዎች ገለጹ። በደስታ የተሞሉ ወታደሮች ጠመንጃቸውን ሲያወዛውዙ፣ ሲጮሁ እንዲሁም ተንበርክከው ሲጸልዩ በማህበራዊ ሚዲያ የተጋሩ እና ቢቢሲ ያረጋገጣቸው ቪዲዮዎች አሳይተዋል።
