በትግራይ ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ 20 ሰዎች መቁሰላቸው ተነገረ
በትግራይ ክልል መዲና መቀለ አቅራቢያ በምትገኘው ሰሐርቲ ወረዳ፣ ረቡዕ፣ የካቲት 12/ 2017 ዓ.ም ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ 20 ሰዎች መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ።

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day
በትግራይ ክልል መዲና መቀለ አቅራቢያ በምትገኘው ሰሐርቲ ወረዳ፣ ረቡዕ፣ የካቲት 12/ 2017 ዓ.ም ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ ቢያንስ 20 ሰዎች መቁሰላቸውን የዓይን እማኞች ተናገሩ።

የኤርትራ መንግሥት የቀድሞ የሠራዊት አባላት ወደ የክፍሎቻቸው ለዳግም ሥልጠና እንዲመለሱ እና ሌሎችም ከአገር እንዳይወጡ የሚያዝ መመሪያ ማስተላለፉን በኤርትራ ውስጥ እና በውጪ ሀገራት የሚገኙ የአገሪቱ ዜጎች ለቢቢሲ አረጋገጡ።

የኢሜግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አርብ፣ የካቲት 14/ 2017 ዓ.ም ይፋ የሚያደርገው አዲሱ ፓስፖርት የጊዜ ገደብ ወደ 10 ዓመት ከፍ ማለቱን የአገልግሎቱ የኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር ማስተዋል ገዳ ለቢቢሲ ተናገሩ።ዳይሬክተሯ ከዚህ በኋላ ዕድሜያቸው ከ25 ዓመት በላይ የሆኑ ዜጎች የማብቂያ ጊዜው 10 ዓመት የሆነውን አዲሱን ፓሰፖርት እንደሚወስዱ ገልጸዋል።

ረጅም ጊዜ ጥቃት ሲያደርሱበት የቆዩትን የአሜሪካ የፌደራል ምርመራ ቢሮ (ኤፍቢአይ) በዳይሬክተርነት እንዲመሩ በሀገሪቱ ሴኔት ሹመታቸው የጸደቀላቸው ካሽ ፓቴል፤ ህግ አስከባሪ ተቋሙን "መልሰው ለመገንባት" ቃል ገቡ።

አሜሪካ አልሳተፍበትም ያለችው የቡድን 20 አባል አገራት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ጉባዔ በደቡብ አፍሪካ ተከፈተ።

በእስራኤል ዋና ከተማ ቴል አቪቭ ደቡባዊ ክፍል ባት ያም፤ ፖሊስ የሽብር ጥቃት እንደሆኑ የጠረጠራቸው ሶስት የአውቶብስ ፍንዳታዎች ማጋጠማቸው ተገለጸ።

ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዘለንስኪ ወደ ድርድሩ ጠረጴዛ ተመልሰው አሜሪካ የዩክሬንን ወሳኝ ማዕድን በምታገኝበት ዙሪያ ስምምነት ላይ እንዲደርሱ የዋይት ሃውስ የብሔራዊ ደህንነት አማካሪ ማይክ ዋልትዝ አስታወቁ።

ተመራማሪዎች የእርጅና ምልክቶችን ለማዘግየት ጥቅም ላይ ሊውሉ ይችላሉ የተባሉ ሳይንሳዊ ግኝቶችን ይፋ አድርገዋል። የተመራማሪዎቹ ቡድን፣ የሰው አካል ከስቴም ሕዋስ እንዴት ቆዳን እንደሚፈጥር እንዲሁም የተወሰነ መጠን ያለው ቆዳን በቤተ ሙከራ ውስጥ ማምረት እንደሚቻል ደርሶበታል።

ማክሰኞ፣ የካቲት 11/ 2017 ዓ.ም አሜሪካ እና ሩሲ በሳዑዲ አረቢያ ያካሄዱት የሰላም ንግግር የሞስኮን ከምዕራቡ ዓለም መገለል የቋጨ ነው። የሁለቱ ተደራዳሪ ቡድን ሦስት አሜሪካዊያንን እና ሦስት ሩሲያዊያንን አካቷል።
