ሂውማን ራይትስ ዎች በትግራይ ክልል "እስከ 15 ዓመት የሆኑ ልጆች" በግዳጅ ተመልምለዋል ሲል ከሰሰ
በትግራይ ክልል ዕድሜያቸው "እስከ 15 የሆኑ ልጆች" ጭምር "እየታፈኑ እና በሕገ ወጥ መንገድ እየተመለመሉ" መሆኑን ዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶች ተሟጋች 'ሂውማት ራይትስ ዎች' ገለጸ። ተቋሙ፤ አሜሪካ እንዲሁም የአውሮፓ እና የአፍሪካ ኅብረቶች "የትግራይ ባለሥልጣናት የግዳጅ ምልመላውን እንዲያቋርጡ እና የተያዙ ልጆችን በሙሉ እንዲለቅቁ" የሚያስችል ጫና እንዲያደርጉ ጠይቋል።









