ኢትዮጵያ የአውሮፓ ኅብረት የዓባይ ውሃን በተመለከተ ከግብፅ ጋር በጋራ ያወጣውን መግለጫ ተቃወመች
በብራሰልስ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ፤ የአውሮፓ ኅብረት ከግብፅ ጋር በመሆን ካይሮ በዓባይ ወንዝ ላይ የምታነሳውን "የቅኝ ግዛት እና የብቸኛ ተቆጣጣሪነት መብት የሚያስተጋባ" መግለጫ አውጥቷል በማለት ወቀሰ። የአውሮፓ ኅብረት እና ግብፅ ያወጡት የጋራ መግለጫ፤ "በኢትዮጵያ ላይ የተሳሳተ፣ አድልዎ ያለበት እና ጠበኛ አቋም" ያሳየ እንደሆነ በመግለጽም ተቃውሞውን አሰምቷል።

