ሰሜን ኮሪያ በቅርቡ ያስመረቀችው ግዙፍ የመዝናኛ ስፍራ ለውጭ ቱሪስቶች እንደማይፈቀድ አሳወቀች
ሰሜን ኮሪያ ከሁለት ሳምንት በፊት በይፋ ያስመረቀችው ግዙፉ ዘመናዊ የባሕር ዳርቻ የመዝናኛ ስፍራ ለውጭ ዜጎች እንደማይፈቀድ አስታወቀች።

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day
ሰሜን ኮሪያ ከሁለት ሳምንት በፊት በይፋ ያስመረቀችው ግዙፉ ዘመናዊ የባሕር ዳርቻ የመዝናኛ ስፍራ ለውጭ ዜጎች እንደማይፈቀድ አስታወቀች።

የብራዚል ፍርድ ቤት በመፈንቅለ መንግሥት ሙከራ የተከሰሱት የቀድሞው ፕሬዚዳንት ጄይር ቦልሶናሮ ሊያመልጡ ይችላሉ በሚል ስጋት በእግራቸው ላይ መከታተያ እንዲያጠልቁ እና የሰዓት እላፊ እንዲጣልባቸው ውሳኔ አሳለፈ።

እንግሊዝ ውስጥ ባለፉት ሳምንታት የፊት ቆዳ መሸብሸብን ለመከላከል በተሰጠ የቦቶክስ የውበት ሕክምና ጥቅም ላይ በዋለ ሐሰተኛ መድኃኒት ምክንያት ከሰላሳ በላይ ሰዎች የመመረዝ ጉዳት እንደደረሰባቸው ተነገረ።

የእስራኤል ጦር በጋዛ ከሚፈጽማቸው ጥቃቶች በተጨማሪ በፍንዳታዎች፣በቡልዶዘሮችና ኤክስካቬተሮች ታግዞ ህንጻዎችን እየደረመሰ ከመሬት ጋር እያመሳሰላቸው ነው። በታቀደ ፈረሳም ህንጻዎቹን ከመሬት ጋር ለማመሳሰል ከአሜሪካ ዲ9 የተሰኙ ቡልዶዘሮችም አግኝቷል።

በእነ አቶ ዮሐንስ ቧያለው መዝገብ ክስ የተመሠረተባቸው ተከሳሾች ለፍርድ ቤት ያቀረቧቸው ቅሬታዎች መፍትሔ ካላገኙ ችሎት እንደማይቀርቡ አስታወቁ።ተከሳሾቹ ይህን ያስታወቁት በዚህ ሳምንት አጋማሽ ጉዳያቸው ለሚታይበት ለፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ለሕገ መንግሥት እና ሽብር ወንጀል ጉዳዮች ችሎት በጽሁፍ ባቀረቡት አቤቱታ ነው።

የአሜሪካ ሴኔት ለውጭ እርዳታ እና ለብሔራዊ ሬድዮዎች ይውል ከነበረው 9 ቢሊዮን ዶላር እንዲቀነስ የቀረበውን ረቂቅ ህግ አጸደቀ።

አምባሳደር ኃይሌ መንቆሪዎስ ኤርትራዊ ዲፕሎማት ሲሆኑ ኤርትራ ነጻ ከወጣች በኋላ አገራቸውን በመወከል በአዲስ አበባ አምባሳደር ነበሩ። ከዚያም በኋላ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት እንዲሁም በአፍሪካ ኅብረት ውስጥ በተለያዩ ኃላፊነቶች ላይ ሠርተዋል። በአፍሪካ ሰላም፣ ደኅንነት እና ልማት ጉዳዮች ላይ አማካሪም ናቸው። በአሁኑ ወቅት በኤርትራ እና በኢትዮጵያ መካከል ያለውን ፍጥጫ በተመለከተ ከቢቢሲ ጋር ቆይታ አድርገዋል።



