ዝነኛው ራፐር ዲዲ ከከባድ ክሶች ነጻ ቢባልም ዋስትና ተከለከለ

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day

በትግራይ ክልል ወጀራት በተባለው ወረዳ በትግራይ ኃይሎች እና በሌሎች ታጣቂዎች መካከል ግጭት መፈጠሩን ቢቢሲ አረጋገጠ። ግጭቱ የተከሰተው በትግራይ ክልል ደቡባዊ ዞን ሰንዓለ የዞኑ አካባቢ በሁለቱ የታጠቁ ኃይሎች መካከል ማክሰኞ ሰኔ 24/2017 ዓ.ም. አመሻሽ ከ10 አስከ 11 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ መሆኑን ነዋሪዎች ተናግረዋል።

ፓንክ እና ራፕን አጣምረው የሚጫወቱት የዩናይትድ ኪንግደሙ ቦብ ቪላን ባንድ ሙዚቀኞች ባለፈው ቅዳሜ በግላስተንበሪ ፌስቲቫል ላይ "ሞት ለእስራኤል ጦር" በሚል መድረክ ላይ ባሰሙት መፈክራቸው ከማንችስተር ሙዚቃ ፌስቲቫል ተሰረዙ።

የ30 ዓመቱ ግለሰብ እንደ አውሮፓውያኑ በ2022 በአሜሪካዋ ኢዳሆ ኮሌጅ ከተማ አራት አብረውት የሚኖሩ ተማሪዎችን መግደሉን አመነ።ግለሰቡ ጥፋቱን ያመነው የሞት ቅጣትን ለማስቀረት ከአቃቤ ህግ ጋር የገባውን ስምምነት ተከትሎ ነው።

እስራኤል በጋዛ የኢንዶኔዥያ ሆስፒታል ዳይሬክተር መኖሪያ ቤት ላይ በፈጸመችው ጥቃት እሳቸውን ጨምሮ በርካታ የቤተሰቦቻቸው አባላት መገደላቸውን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ገለጸ።


ኤርትራ ተጥሎባት የነበረው የጦር መሳሪያ ማዕቀብ መነሳቱን ተከትሎ ሠራዊቷን መልሳ በማጠናከር በአካባቢው በተለይም በኢትዮጵያን መረጋጋት እንዳይኖር እያደረገች ነው ሲል አንድ የአሜሪካ መንግሥታዊ ያልሆነ ድርጅት ሪፖርት አመለከተ። ኤርትራ ግን የቀረበባት ክስ የፈጠራ እና ማሳበቢያ ነው በማለት በአካባቢው ለተፈጠረው ውጥረት ተጠያቂያዋ ኢትዮጵያ ናት ስትል ከስሳለች።

በሐዋሳ ኢንዱስትሪ ፓርክ ትናንት ማክሰኞ፣ ሰኔ 24/2017 ዓ.ም. በተከሰተ "የቦይለር ፍንዳታ" አደጋ የሁለት ሰዎች ሕይወታቸው ሲያልፍ ሁለት ሰዎች ደግሞ መቁሰላቸው ተነገረ። ፍንዳታው የተከሰው በኢንዱስትሪ ፓርኩ ውስጥ የወረቀት ማሸጊያ አምራች በሆነው ጃስ ሆልዲንግ በተባለ የአገር ውስጥ ኩባንያ ውስጥ ነው።


ስምንትን ሰዎችን አሳፍሮ የነበረ የኡጋንዳ ወታደራዊ ሄሊኮፕተር በሶማሊያ መዲና ሞቃዲሾ ዋና አለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ረቡዕ፣ ሰኔ 25/ 2017 ዓ.ም መከስከሱን የሶማሊያ አቪዬሽን ባለስልጣን ለቢቢሲ ተናገሩ።
