አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጠውን ወታደራዊ እርዳታ አቋረጠች
አሜሪካ ለዩክሬን የምትሰጠውን ወታደራዊ እርዳታ ማቋረጧን የዋይት ሐውስ ባለስልጣናት በአሜሪካ የቢቢሲ አጋር ለሆነው ሲቢኤስ ኒውስ አረጋገጡ። አንድ የዋይት ሐውስ ባለስልጣን "ፕሬዝዳንቱ ሙሉ ትኩረታቸው ሰላም ላይ ነው። አጋሮቻችንም እዚህ ግብ ላይ እንዲያተኩሩ እንፈልጋለን። የምናደርገውን እርዳታ ለጊዜው አቁመን ለመፍትሄው የሚኖረውን አበርክቶ መለስ ብለን ለመፈተሽ እንፈልጋለን" ብለዋል።

