ወደ ህዋ ሊመጥቅ ሲል የፈነዳው የስፔስኤክስ ሮኬት ስብርባሪዎች በረራዎችን አስተጓጎሉ
ሐሙስ ዕለት ከቴክሳስ ወደ ህዋ ለመምጠቅ የተነሳው የስፔስኤክስ ሮኬት ፈንድቶ ስብርባሪዎቹ በረራዎችን አስተጓጎሉ።

The latest stories from Ethiopia's trusted newsrooms, gathered in one place.
Updated throughout the day
ሐሙስ ዕለት ከቴክሳስ ወደ ህዋ ለመምጠቅ የተነሳው የስፔስኤክስ ሮኬት ፈንድቶ ስብርባሪዎቹ በረራዎችን አስተጓጎሉ።

ባለፉት ዓመታት በአዲስ አበባ በቅርስነት ተመዝግበው የነበሩ እንዲሁም ሌሎችም ታሪካዊ ሕንጻዎች፣ ቤቶች እና አካባቢዎች እንደ ዋዛ አፈር ለብሰዋል። በምትካቸው ሰማይ ጠቀስ ፎቆች ሊቆሙ አፈራቸው እየተማሰ ነው፤ ቀን ከሌት። ጥድፊያው ነጠላ ለመዘቅዘቅ ጊዜ አይሰጥም። በዚህ ዘገባ፣ አንድን ሕንጻ ወይም ቤት ቅርስ አልያም ታሪካዊ ሥፍራ ለማለት መስፈርቱ ምንድን ነው? የታሪካዊ ሕንጻዎች እና ቤቶች መፍረስ በታሪክ፣ በነዋሪዎች ሥነ ልቦና፣ በኪነ ሕንጻ እና በማኅበራዊ መስተጋብር ላይ ምን ጫና ያሳድራል? ቅርሶች እና ታሪካዊ ሥፍራዎችን እንዴት ጠብቆ ማደስ፣ ማዘመን፣ መልሰው አገልግሎት ላይ እንዲውሉ ማድረግ እንዲሁም ከሌሎች ግንባታዎች ጋር ጎን ለጎን እንዲሄዱ ማድረግ ይቻላል? የሚሉት እና ተያያዥ ነጥቦች ይዳሰሳሉ።

የዩክሬኑ ፕሬዚዳንት ቮሎድሚር ዜሌንስኪ አገራቸው ከአሜሪካ ጋር በመጪው ሳምንት በሳዑዲ አረቢያ ልታደርገው ያቀደችው ውይይት "ትርጉም ያለው" እንደሚሆን ተስፋቸውን ገለጹ።

ታዳጊ ወንዶችን ደፍሯል የተባለው የጋቦን ታዳጊ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ የህይወት ዘመን እገዳ ተጣለበት

በደቡብ ኮሪያ ተዋጊ ጄቶች በስህተት ስምንት ቦምቦች በመኖሪያ ስፍራዎች መጣላቸውን ተከትሎ 15 ሰዎች መጎዳታቸውን የሃገር ውስጥ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።


ፓላንዳዊቷ ዶ/ር ኤቫን የአማርኛ ቋንቋን ከ40 ዓመት በፊት ተምራ በዲግሪ ከተመረቀች በኋላ ከሃያ ዓመታት በላይ በማስተማር በርካቶችን በአማርኛ ቋንቋ ዲግሪ አስይዛለች። የምታስተምርበት ዩኒቨርስቲ ወደ 80 ዓመታት ለሚጠጋ ጊዜ አማርኛን እያስተማረ ነው። አማርኛ ቋንቋን “ፏፏቴ ነው” የምትለው ዶ/ር ኤቫን በአገሯ በአማርኛ አስተርጓሚነት ትሠራለች። ለመሆኑ እንዴት ከአማርኛ ጋር ተዋወቀች?

የደቡብ ሱዳን ዋነኛ ተቃዋሚ ፓርቲ ወታደራዊ ክንፍ የጦር አዛዥ ጄነራል መታሰር ለአምስት ዓመታት የዘለቀውን የእርስ በርስ ጦርነት የቋጨውን የሰላም ስምምነት "የጣሰ ነው" ሲሉ የተቃዋሚው ቃለ አቀባይ ተናገሩ።

የአሜሪካ አቃቤ ሕጎች በአገሪቱ የሚገኙ የቻይና መንግሥት ተቃዋሚዎችን መረጃ በመመንተፍ ለቤጂንግ መንግሥት በመሸጥ የተጠረጠሩ 12 ቻይናውያን ላይ ክስ መሰረቱ። የአሜሪካ ፍትህ ሚኒስቴር መረጃ እንደሚያመለክተው፤ "በመንግሥት የተደገፈው" የሳይበር ጥቃት የአሜሪካ መንግሥት ተቋማት ላይም ያነጣጠረ ነበር።

ቻይና ለወታደራዊ በጀት ብቻ 245 ቢሊዮን ዶላር ብትመድብም ከአሜሪካ በጣም ያነሰ ነው። የስቶክሆልም ዓለም አቀፍ የሰላም ምርምር ኢንስቲትዩት እንዳለው ቻይና ምንም እንኳ ከአሜሪካ እና ሩሲያ በጣም ያነሰ ቢሆንም 1.6 በመቶ የሚሆነውን የአገር ውስጥ ምርቷን ለወታደራዊ አገልግሎት ታወጣለች። ይኹን እንጂ ተንታኞች ቻይና ለመከላከያ የምታወጣውን ገንዘብ ዝቅ አድርጋ ታቀርባለች ብለው ያምናሉ።
